የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት
የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት የሃገራችን ህዝብ በጥራት ላይ የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖረው ለማድረግ የተቋቋመ ድርጅት ነው::
የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት የሃገራችን ህዝብ በጥራት ላይ የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖረው ለማድረግ የተቋቋመ ድርጅት ነው::
ድርጅታችን የሚሰራው ሰዎችን እና አካባቢን እንዲሁም በንብረት ላይ ከሚመጣ ከጨረር ጉዳት መከላከል ነው:: የጨረራ ክስተቶችና አደጋዎች(Radiological incidents & Accident) የጨረራ አደጋ ወይንም ራዴሽን አክሲደንት ስንል ባልተጠበቀ ሁኔታ ለአይዮን ፈጣሪ የጨረራ አመንጪ ቁሶች መጋለጥ ነው፡፡ ይህ አደጋ በተጨባጭ ወይንም ተጨባጭ ባልሆነ መልኩ ሊከሠት ይችላል፡፡ የራዲዮሎጂካል አደጋዎች የሚከሠቱት የትና እንዴት ነው? የራዲዮሎጂካል አደጋዎች የሚፈጠሩት የጨረር ቁስ ባለበት ቦታ ሲሆን የሚከተሉት ይገኙበታል፡፡ 1. በህክምና ማዕከላት፡-ይኸውም ሰዎች የጨረራ ህክምና ለማድረግ ሲመጡ የሚወስዱት የጨረራ ዶዝ ከፍተኛ ከሆነ ለጨረራ ሊጋለጡ ይችላሉ፡፡ 2. ጥራትን ለመፈተሽ በመጠጥና በምግብ ፋብሪካዎች አካባቢ የኢንዱስትሪያል ራዲዮግራፊ ተግባራት በሚካሄዱበት ወቅት 3. በትምህርትና ምርምር ማዕከላት ለምሣሌ በቤተ ሙከራ ውስጥ በሚካሄዱ የላቦራቶሪ ፍተሻዎች 4. የራዲዮአክቲቭ ቁሶች ከቦታ ቦታ ሲዘዋወሩ ተገቢው ጥንቃቄ ሳይደረግ ሲቀር፤ 5. በመስክ ላይ በሚደረግ የተግባር ፍተሻ 6. የኒውክለር ሪሰርች ሪአክተር ሲገነባና እና በመሣሠሉት ቦታዎች የራዲዮሎጂካል አደጋዎች ሊከሠቱ ይችላሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የራዲዮአክቲቭ ቁሶች በአሸባሪዎች እጅ ከገቡ የጨረራ አደጋ ሊከሠት ይችላል፡፡ የራዲዮሎጂካል አደጋዎች የሚያስከትሏቸው ውጤቶች፤ በአንድ ሀገር ውስጥ የሚፈጠር የራዲዮሎጂካል አደጋ ሊያስከትለው የሚችለው ጠንቅ ከሀገሩ አልፎ ለጐረቤት ሀገሮችም ከፍተኛ ጫና የመፍጠር አቅም አለው፡፡ ጥቂቶቹን ለመዘርዘር ብንሞክር፣ የጤና፣ የምጣኔ ሀብት፣ የፖለቲካ፣ የማህበራዊ፣ ስነልቦናዊ፣ ህጋዊና የተፈጥሮ ብክለት ችግሮች በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሣሉ፡፡ ጥናቶች እንደሚያመላክቱት በተለያዩ ወቅቶች በአለማችን ሀገሮች ዘንድ የጨረራ አደጋዎች ተከስተው ትልቅ የህይወትና የንብረት ውድመት አስከትለዋል፡፡ ከዚሁ ጋር ተያይዘው በየሀገሩ የሚደረጉ የኒውክለር ሙከራዎች በሠውና አካባቢ ደህንነት ላይ ትልቅ ስጋት ፈጥረዋል፡፡ • ለአብነት ብንጠቅስ፡- NRX Canada,1952, USA 1960, Switzerland 1976 ፣ USSR 1986, japan 2011, የራዲዮሎጂካል አደጋዎች በቀዳሚነት ይነሳሉ፡፡ አደጋዎች ከማጋጠማቸው በፊት የመከላከያ እቅዶች /Preparedness plan Response / እንዲኖሩ ማድረግ እጅግ ወሣኝ ጉዳይ ነው፡፡ የእቅዱ መዘጋጀት ሁለት ዋና ዋና ጠቀሜታዎች ይኖሩታል 1. በትክክለኛ ጊዜ ትክክለኛ ዕቅድ በማውጣት ህይወትና አካባቢን ከአደጋ ለመታደግ እና 2. አደጋውን በመቀነስ ከፍተኛ ወጪን ለማስቀረት ያግዛል በአጠቃላይ የራዲዮሎጂካል አደጋዎች እንዳይከሠቱ በመከላከል የህክምና ባለሙያዎችና የጨረራ ሠራተኞች ከፍተኛ ሀላፊነት እንዳለባቸው አውቀው ከባለሥልጣኑ ጐን በመቆም አደጋውን ለመቀነስ መረባረብ የትኩረት ጉዳይ ይሆናል፡፡
ዘመናዊ የባቡር መሠረተ ልማት እና አገልግሎት አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ኢኮኖሚ ግንባታ ኢትዮጵያ ጥረት የሚደግፍ ቀልጣፋ የባቡር ኩባንያ ለማየት, በዚያ ኤሌክትሪክ ይጠቀማል እንዲሁም ከጎረቤት አገሮች ወደቦች ጋር በሀገሪቱ የልማት ማዕከላት እና አገናኞች ያገናኛል.
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በ 1935 በመንግስት አዋጅ የኢትዮ ጣልያን ጦርነትን ተከትሎ ተመሰረተ::በተመሰረተ በጥቂት ወራት ውስጥ 300 የመጀመሪያ እርዳታ ሰጪዎች እና 6 አምፑላንሶች ወደ የጦር ሜዳዎች የተጎዱትን ለመርዳት አሰማርቷል::
የኢትዮጲያ መንገድ ግንባታ ኮርፖሬሽን የሚታወቀው ደረጃቸውን የጠበቁ፣ ለመንገዱ አስፈላጊ የሆኑት ነገሮችን አሟልቶ ስለሚያስረክብ ነው
የኢትዮጵያ ገጠር ኢነርጂ ልማት ማስፋፊያ ማዕከል
የኢትዮጵያ ስፌት ክር ፋብሪካ አ.ማ
የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ድርጅት - ጭነት ማስተላለፍ ዘርፍ