የኢትዮጲያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ
ከደርግ መንግሥት መውደቅ ማግሥት የሽግግር መንግሥት የተቋቋመ ሲሆን የሽግግር መንግስቱን ቻርተር መሠረት በማድረግ የምርጫ ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር 11/1984 ዓ.ም ወጣ፡፡ የምርጫ ኮሚሽን በየካቲት ወር 1984 ዓ.ም በወረዳና በቀበሌ ደረጃ የጊዜያዊ አስተዳደር ኮሚቴ አባላት ምርጫ አከናወነ በመቀጠልም በግንቦት ወር 1984 ዓ.ም የብሔራዊ፣ ክልላዊና የወረዳ ምክር ቤቶች አባላት ምርጫ አካሂዷል፡፡