Search results for - bahirdar

  • የአማራ ብሔራዊ ክልል መንግስት ፍትህ ቢሮ

    Governmental Organizations

    ተልዕኮ የክልል ምክር ቤት የክልሉ ህዝቦች ሉዓላዊ ሥልጣን መገለጫ በመሆኑ በምክር ቤቱ አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴ ላይ የህዝብ ተሳትፎ እንዲጎለብት ማድረግ ፣ የምክር ቤቱ ጉባኤዎች በበቂ ዝግጅት ወቅቱን ጠብቀው እንዲካሄዱ ማስቻል ፣የሃገሪቱንና የክልሉን ህግጋተ መንግስታት ፣ ፖሊሲዎች ፣ ስትራቴጅዎች ፣ በምክር ቤቱ የሚወጡ ህጎችን ተግባራዊነት ማረጋገጥ እና የምክር ቤቶችን አቅም ማጠናከር፡፡

    058 220 0917
  • አማራ ብሔራዊ ክልል መንግስት የፍትህ ባለሙያዎች ማሰልጠኛ እና የህግ ምርምር ኢንስቲትዩት

    Governmental Organizations

    ክልሉ ፍትህ ስርዓት ለህገ መንግስታዊ ስርዓቱ በጽናት በሚቆሙ፣ ለህዝብ መብትና ጥቅም በሚቆረቆሩ፣ በእውቀት፣ በክህሎትና በስነምግባር በታነጹ ሙያተኞች የተገነባና ፍትህ ስርዓቱን ተደራሽ ፣ ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ ጥራትና ብቃት ያለው በፍላጎት ላይ የተመሰረተ ስልጠና በመስጠትና ጥናትና ምርምር በማካሄድ ለፍትህ ስርዓቱ መጎልበት አስተዋፅኦ ማድረግ

    058 226 0122
  • የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አመራር አካዳሚ

    Governmental Organizations

    የአማራ ብሔራዊይ ክልላዊ መንግስት አመራር አካዳሚ ተልዕኮ ክልሉን ሊያሣድጉ የሚችሉ ብስለት ያላቸውን ሣይንሳዊና ዘመን ተሻጋሪ ሃሳቦች በማመንጨት የትምህርትና ስልጠና፣ የምርምርና ምክር አገልግሎት በመስጠት የህዳሴውን ጉዞ ቀጣይነት የሚያረጋግጥ፣የህዝብን ጥያቄ ፈጥኖ የሚረዳና ምላሽ የሚሰጥ ብቃት ያለው የፖለቲካ አመራርና ሌሎች የልማት ኃይሎችን በማፍራት ለሃገሪቱ ዘላቂ ልማትና ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ አስተዋጽኦ ማድረግ ነው ፡፡ ራዕይ አካዳሚው በ2017 በፖለቲካዊ አመራር ጥበብ በአገር ደረጃ የለውጥና የብቃት ሞዴል ማዕከል ሆኖ ማየት፣ የአመራር አካዳሚው ሥልጣንና ተግባር አካዳሚው የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባራት አሉት  በሀገሪቱ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ዙሪያ የየደረጃውን አመራርና ፈፃሚ ሀይሎች በብቃትና በጥራት ለማፍራት የሚያስችሉና በዘመናዊ የጥናት፣ የምርምር፣ የምልከታ፣ የትንተና እና የሥርፀት ሥራዎች የተደገፉ የአጭር፣ የመካከለኛና የረዥም ጊዜ ትምህርትና ስልጠናዎችን ይሰጣል፣ ለዚሁ የሚያገለግሉ ሞጁሎችን ያዘጋጃል፣ ሌሎች ተያያዥነት ያላቸውን የትምህርት መርጃ መሳሪያዎች ያደራጃል፤  ክልላዊ እና ሀገር አቀፍ የልማት ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችን፣ መርሆዎችንና ዓላማዎችን መነሻ በማድረግ ዝርዝር የትምህርትና የስልጠና መርሀ-ግብሮችን ይቀርፃል፣ በቦርዱ ሲፀድቁለትም በስራ ላይ እንዲውሉ ያደርጋል፤  የሚሰጣቸውን የትምህርትና የስልጠና መርሀ-ግብሮች ተከታትለው ላጠናቀቁ እጩ ምሩቃን የምስክር ወረቀትና እንደ ተገቢነቱ በሀገሪቱ የከፍተኛ ትምህርት አዋጅ ቁጥር 650/2001 ሌሎች ተዛማጅ ህጐች መሠረት ዲፐሎማ ወይም ዲግሪ ይሰጣል፤  የራሱን የትምህርትና ስልጠና አሰጣጥ በየጊዜው ለማሻሻልም ሆነ የክልሉን መንግስታዊ ተቋማት የማስፈፀም አቅም ለመገንባት የሚረዱ የጥናትና የምርምር ስራዎችን ያካሂዳል፤  ከመንግስታዊ መ/ቤቶች ወይም ተቋማት፣ ከመንግስት የልማት ድርጅቶችና ከግሉ ዘርፍ በሚቀርብለት ጥያቄ መሰረት በአመራር ፍልስፍናና በሥነ-ምግባር ግንባታ ላይ ያተኮሩ ስልጠናዎችንና የምክር አገልግሎቶችን ይሰጣል፤  በየጊዜው የሚሰጣቸውን ትምህርትና ስልጠናዎች በተመለከተ የግምገማና የምዘና ሥርዓት ቀርጾ በተግባር ላይ እንዲውል ያደርጋል፤  በክልሉ መንግስት መስሪያ ቤቶች የሚያገለግሉ ባለሙያዎችን የሥራ አመራር ብቃት ለማጎልበትና ለማሳደግ የሚረዱ የአጭርና የመካከለኛ ጊዜ ስልጠናዎችን ይነድፋል፣ ያሰለጥናል፣  በጥናትና ምርምር ስራዎች የተገኙ ውጤቶችን ያሳትማል፣ ለተጠቃሚዎች ያሰራጫል፤  ቦርዱ በሚያወጣቸው የምልመላ መስፈርቶች መሰረት ሰልጣኞችን ይቀበላል፣ የዕለት ተዕለት ግንባታቸውን በቅርብ ይከታተላል፤  በስሩ የተለያዩ የትምህርት፣ የስልጠና፣ የጥናትና የምርምር ክፍሎችን ያቋቁማል፣ የቤተ-መፃሀፍትና የቤተ-ሙከራ አገልግሎቶችን ያደራጃል፣ ተፈላጊ ግብዓቶች እንዲሟሉላቸው ያደርጋል፤  ሰልጣኞች የተሰጣቸውን ስልጠና አጠናቀው ወደየስራቦታቸው ሲመለሱ የሚኖራቸውን አፈፃፀም በቅርብ ይከታተላል፣ የስልጠና ዉጤታማነት ጥናት ያካሂዳል፣ ግኝቱን በተመለከተ ለሚመለከተዉ አካል ሪፖርት ያደርጋል፣ ከዚሁ በመነሳት የተሻሉ የአሰራር ስልቶችን ይቀይሳል፤  የተለያዩ ትምህርታዊ ሴሚናሮችን፣ ወርክ ሾፖችን፣ ኮንፈረንሶችንና አውደ- ጥናቶችን ያዘጋጃል፣ ያካሂዳል፣ ጥሪ ሲደረግለትም በንደነዚህ ዓይነት መድረኮች ይሳተፋል፤  አቻዎቹ ከሆኑና ተቀራራቢ ዓላማ ካላቸው የክልልና የፌደራል መንግስት ተቋማት ጋር የስራ ግንኙነቶችን ይመሰርታል፣ በትብብር ስልጠና ይሰጣል፣ ከሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ መርሆዎችና ዓላማዎች ጋር በተጣጣመ ሁኔታ በዉጭ ሀገር ከሚገኙ መሰል የስልጠናና የምርምር ተቋማት ጋር ሊገናኝና ተሞክሮዎችን ሊለዋወጥ ይችላል፤  የሥራ አመራር ሥልጠና፣ የምክር አገልግሎትና የጥናት ፕሮጀክቶችን በማዘጋጀት ገቢ የሚያገኝባቸዉን ሁኔታዎች ያመቻቻል፣ ለሚሰጣቸው አገልግሎቶች እንደአስፈላጊነቱ ተመጣጣኝ ዋጋ ያስከፍላል፤  የንብረት ባለቤት ይሆናል፣ ዉሎችን ይዋዋላል፣ በስሙ ይከሳል፣ ይከሰሳል፤  ዓላማዎቹን ከግብ ለማድረስ የሚረዱ ሌሎች ተዛማጅ ተግባራትን ያከናውናል፡፡

    058 320 5065 www.ala.edu.et
  • አማራ የማዕድን ሀብት ልማት ማስፋፊያ

    Mining

    የክልሉን የማዕድን ሃብት ዓይነተና ክምችት በማጥናትና ሰፊ የማስተዋወቅ ሥራ በማካሄድ ዜጎች በዘላቂው የማዕድን ሃብት ልማት እንዲሳተፉ ,በማድረግ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ፣

    058 220 4845
  • Amhara National Regional State Office of Government

    Governmental Organizations

    በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት

    058 220 0923
  • Amhara National Regional State Police Commission

    244

    የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ፖሊስ ኮሚሽን

    058 220 1327
  • የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስትማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን

    P.O.Box 3502 Bahir Dar, Ethiopia

    በፍርድ ቤት ትዕዛዝ የሚላኩ ታራሚዎችና የመደበኛ ቀጠሮ እስረኞችን ተረክቦ ተገቢውን የባህሪ ለውጥ እንዲያመጡ የጥበቃ ፤ የእርምትና የሙያ ክህሎት ስልጠና አገልግሎቶችን በማቅረብ የታረሙ የሰለጠኑና ሰላማዊ ዜጋ እንዲሆኑ ማስቻል ነው።

    058 220 1107