Governmental Organizations
የዞኑ ገጽታ
የምስራቅ ጐጃም ዞን በአማራ ክልል ከሚገኙ 10 ዞኖች መካከል በኢንቨስትመንት ፍሰቱ ግንባር ቀደም ከሆኑት ውስጥ የሚመደብ ሲሆን በሰሜን ከደቡብ ጐንደር፣ በደቡብ ኦሮሚያ ክልል፣ በምዕራብ ከምዕራብ ጐጃም እንዲሁም በምስራቅ ከደቡብ ወሎ ይዋሰናል፡፡ የመሬት ከፍታውም ዝቅተኛ 500 ከፍተኛ 4154 ሜትር ሆኖ ዓመታዊ ዝናብ መጠኑም በአማካይ ከ900 – 180ሚ.ሜ ይደርሳል፡፡
የዞኑ ዝቅተኛው የሙቀት መጠን 10 ሲ.ግ ከፍተኛ ደግሞ 30 ሴ.ግ፣ የአየር ንብረት 16% ቆላማ፣ 45%፣ ደጋ 37% ወይናደጋ 2% ውርጭ የተከፋፈለ ሆኖ የመሬት አቀማመጡም 39% ተራራማ፣ 12% ደግሞ ሸለቆማ ነው፡፡ አጠቃላይ የዞኑ የቆዳ ስፋትም የክልሉን 8.6% ያህሉን የሚሸፍን ሆኖ 1400.74 እስኮየር ኪ.ሜ ሲሆን በ4 ከተማ አስተዳደሮችና በ17 ወረዳዎች የተከፋፈለ ነው፡፡
1. የዞኑ የኢንቨስትመንትት እንቅስቃሴ
በዞናችን ከ1985 – 2009 ባሉት ዓመታታ በተናጠልና በማህበር በኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ወስጥ ተሳታፊ ለመሆን 15,189,961,919 ብር ካፒታል ካስመዘገቡ 839 ኘሮጀክቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ የተሰጠ ሲሆን የኢንሸስትመንት ፍቃድ ያመጡት በዋና ዋና ኢኮኖሚ ዘርፎች ውስጥ የተሳተፉ ሲሆን እነዚህም ግብርና 270 ሆቴልና ቱሪዝም 94 ኮንስትራክሽን 175 ኢንዱስትሪ 109 ማህበራዊ አገልግሎት 45 ንግድ 139 እና ማዕድን 7 ናቸው፡፡ ፈቃድ ከወሰዱት መካከልም 495 ኘሮጀክቶች ወደ አገልግሎትና ምርት ማምረት 230 ኘሮጀክቶች ደግሞ በዝግጅት ላይ ሲሆኑ ቀሪዎች በዝግጅት ላይ ናቸው፡፡ እነዚህ ኘሮጀክቶችም ለ105,567 የስራ እድል የፈጠሩ ሲሆን ሁሉም ኘሮጀክቶች ተጠናቀው ወደ ስራ ሲገቡ ለ14,4091 የሰው ሃይል ስራ እድል ይፈጥራሉ፡፡
1.1 የኢንቨስትመንት ሀብት በዞናችን
ባለሀብቱን በኢንቨስትመንት በተለይም በኢንዱስትሪ ልማት ዘርፍ ሊያሳትፍ የሚችሉና ለልዩ ልዩ ኢንዳስትሪዎች በግብዓትነት የሚያገለገሉ ጥሬ ሀብቶች በሚፈለገው መጠን ማለትም ጤፍ፣ ስንዴ፣ በቆሎ ሌሎችም የዳልጋ ከብት፣ የበግና ፍየል፣ ዶሮ የወተት ምርት ፣ የማር ምርት ለዓመት ለገቢያ የሚቀርበው ከፍተኛ በመሆኑ ከዚህ በተጨማሪ እጣንና ሙጫ ጨምሮ በደን የተሸፈነ መሬት ያለው ዞን በመሆኑ ባለሀብቱ በነዚህና በሌሎችም ዘርፎች መሰማራት የሚችል ምቹ ሁኔታ አለ፡፡ በዞናችን በአካባቢው ያለውን ጥሬ እቃ ከግምት ውስጥ በማስገባት የተለያዩ የማምረቻ ኢንዱስትሪዎች በመቋቋም ላይ ናቸው፡፡
2. ግብርናና እንስስሳ ሀብትን በተመለከተ ዞኑ ያለበት ሁኔታ
በዞናችን ባሉ ወረዳዎች በግብርና ዘርፍ ዋና ዋና ሰብሎች ጤፍ፣ ስንዴ፣ በቆሎ፣ ቦሎቄ ሰሊጥ በስፋት ይመረታል፡፡ ከአጠቃላይ ምርትና በአማካይ 22.8 ኩ/ል በሄ/ር የሚመረት ሲሆን በአጠቃላይ በዞኑ 15,181,580 ምርት የተመረተ ሲሆን ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በእድገት 884,864 ኩ/ል ጭማሪ አለ፡፡ ለዞኑ የተሰራጨ ግብዓትም 872,000 ኩ/ል ማዳበሪያ ተሰራጨ ሲሆን ከባለፈው ዓመት በልዩነት 119,000 እድገት አለው፡፡
እንስሳት ሀብትን በተመለከተ ከዓመት ዓመት ምርቱ እየጨመረ በመሆኑ የዳልጋ ከብት 1,914,036 በግ 1,979,332 ፍየል 644,208 ፣ ዶሮ 818,273 የጋማ ከብት 351,230 በንብ የተመላ መንጋ 143,688 ያለ ሲሆን በዓመት ሊመረት የሚችል ስጋ ምርት 92,603 ቶን ወተት 126,521 ቶን እንቁላል 42ቶን ቆዳና ሌጦ 81,053ቶን ምርት እንደሚመረት መረጃዎች ያለመለክታሉ
ለኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታዎች በዞናችን
ዞኑ በርካታ የተማረ የሰው ሃይል ያለበትና ስራ ወዳድ ህዝብ ያለበት መሆኑ፣
ልዩ ትኩረት የሚሰጣቸው የማምረቻ እንዱስትሪ ዘርፎች ለተሰማሩ ኘሮጀክቶች ከ2-6 ዓመት ነፃ ግብር መሰጠቱ
በገጠር በእርሻ ስራ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች በአነስተኛ መሬት ኪራይ ተመን መሬት ለኢንቨስትመንት ልማት ይውላል፡፡ በመሆኑም በዞናችን ውሰጥ በሚገኙ ወረዳዎች /አዋበል፣ ጐዘምን፣ ደ/ኤልያስ፣ ደጀን፣ አነደድና ባሶሊበን፣ ወረዳዎች ቆላማ አካባቢዎች ለግብርና ኢንቨስትመንት ሊውል የሚችል መሬት መኖሩ ከዚህም በላይ የመሬት ባለቤት ከሆነው አርሶ አደር በውል ስምምነት በመከራየት ማልመት የሚቻልበት አሰራር ተዘርግቷል፡፡
በኢንዱስትሪ ልማት ዘርፍ የሚሰማሩ ባለሀብቶች ለማበረታታት በዘርፉ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የመሰረተ ልማት ወጭአቸውን በመሸፈን ያላቸውን ውሰጥ ካፒታል በቀጥታ ላሰቡት ኘሮጀክቶች ብቻ እንዲያውሉት ለማድረግ ከፍተኛ በጀት በመመደብ በደ/ማርቆስና በደጀን ከተማ አስተዳደሮች የኢንዱስትሪ መንደሮችን አልምቶ መሬት በምደባ በዝቀተኛ የሊዝ ዋጋ ለባለሀብቱ በማስተላለፍ ዘርፉን በመደገፍ ላይ ይገኛል፡፡
ከኢንዱስትሪ ውጭ ለሆኑ ዘርፎች በአዲሱ የሊዝ አዋጅ መሰረት በጫራታና በምደባ የሚተላለፍ መሬት በየከተሞች እየተለየ ይገኛል፡፡
ዞናችን የአፍሪካ የውሃ ማማ የሆነው የጮቄ ተራራ መገኛ መሆኑ፣
ይህም ለቱሪዝም መስብ ተስማሚ አካባቢ መሆኑ
በርካታ የደጋ ፍራፍሬች የሚበቅሉበት አካባቢ መሆኑ
ወደ ዞናችን መጥተው ለሚያለሙ ባለሀብቶች ከፀጋችን እስከ አገልግሎት ቅልጥፍናችን የተመቸ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
የምስ/ጐ/ዞን አስ/ጽ/ቤት